15262
ይህ ቲቃ (ታማኝ) ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ጨምሮ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ገጽ ነው።
ኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት ከወርቅ ገበያ 2.57 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ።
በእነዚህ አስር ወራት ውስጥ 29,396 ኪሎግራም ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ መቅረቡን የማዕድን ሚኒስቴር አመላክቷል።
በሚኒስቴሩ መረጃ መሰረት ከትግራይ ክልል 12,210 ኪግ፣ ከኦሮሚያ ክልል 6910 ኪግ፣ ከጋምቤላ ክልል 4590 ኪግ እንድሁም ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል 3689 ኪግ ወርቅ ገቢ ተደርጓል። #sputnikafrica
@ThiqahEth
"'እስራኤል የዘር ጭፍጨፋ ታደርጋለች፣ የጦር ወንጀል ትሰራለች' የሚለው ውንጀላ ወደ ጥይት ተቀይሮ እነሆ ዋሽንግተን ላይ ሁለት ዲፕሎማቶች እንደተገደሉ እናውቃለን" - አምባሳደሩ
ከቲቃህ ኢትዮጵናያ ጋር ቆይታ የነበራቸው በኢትዮጵያ የእስራኤም ኤምባሲ አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ አክለው ምን አሉ?
"ሀማስ እስኪደመሰስ ድረስ እስራኤል" ጦርነቱን እንደምትቀጥል አስረግጠው ተናግረዋል።
ምን አሉ? "ሌሎች ሀገራት በእስራኤል ላይ የሚያቀርቡት ትችት በእውነቱ ፀብ አጫሪው ቡድን የያዛቸውን ልቀቁ በማለት ፈንታ እስራኤልን ለምን ተከላከልሽ ብለው ይወነጅላሉ።
ይሄ እውነት የጎደለው ነው፤ ኢ-ኢፍትሀዊ ስለሆነ፣ ሀማስ እስኪደመሰስ ድረስ እስራኤል ምንጊዜም ደህንነቷን ለማስጠበቅ ጦርነቱን ትቀጥላለች።
ሌላው እጅግ በጣም የሚያሳዝነው እስራኤልን በሀሰት የሚወነጅሉ፣ 'እስራኤል የዘር ጭፍጨፋ ታደርጋለች፣ የጦር ወንጀል ትሰራለች' የሚለው ውንጀላ ወደ ጥይት ተቀይሮ እነሆ ዋሽንግተን ላይም ሁለት ድፕሎማቶች እንደተገደሉ እናውቃለን።
ይሄ በሀሰት የሚደረገው ቅስቀሳና ለእስራኤል መጥፎ ስም የሚሰጡ አካላት ውጤት ነው። ስለዚህ እስራኤል ምንጊዜም ቢሆን ህልውናዋን ለማስቀጠል ጦርነቱን ትቀጥላለች ማለት ነው" ብለዋል።
@ByThiqahEthReporter @ThiqahEth
#አማራክልል #እገታ
“በ10 ቀናት ብቻ በአማራ ክልል 31 ሹፌሮችና ረዳቶች ታግተዋል” - ማኀበሩ
ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር፣ “በ10 ቀናት ብቻ በአማራ ክልል 31 ሹፌሮችና ረዳቶች ታግተዋል” ሲል ነግሮናል።
"ገንዘብ ከፍለው የሚወጡ አሉ፤ ነገር ግን ማስፈራሪያ ስለሚደርስባቸው ከወጡ በኋላ የገጠማቸውን የመናገር ድፍረት አይኖራቸውም። ምንክንያቱም ተመልሰው በዚያው መንገድ ነው የሚያሽከረክሩት። የሕግ ከለላ የላቸውም" ብሏል።
በምዕራብ ጎጃም ዞን ቢኮሎና ዱርቤቴ መካከል ባለ ቦታ ግንቦት 17/2017 ዓ/ም አራት ሹፌሮችና አራት ረዳቶች መታገታቸውን ገልጾ፣ “በየቦታው ያለው ነገር ከባድ ነው። ከቀን ቀን እየከፋ፣ እገታ ባልተለመደባቸው ቦታዎች ሁሉ እየተስፋፋ ነው” ብሏል።
በደብረ ብርሃን መንገድ፣ እንጅባራ፣ ቻግኒ በቅርቡ እገታ መፈጸሙን ጠቅሶ፣ “ደቡብ ጎንደር ከጋይንት እስከ ወረታ መገንጠያ ከባድ መንገድ ሆኗል፤ ለየት ባለ መልኩ እገታ ይፈጸምበታል” ነው ያለው።
ማኀበሩ፣ “ድሮ 24 ሰዓት ይነዳባቸው በነበሩ መንገዶች አሁን ሙሉ ለሙሉ ቆሟል። በቀን ለ10 ሰዓታት ነው የሚነዳው። በዚህ ሳቢያ የግድያ ጥቃቱ ቀንሷል። እገታው ግን በጣሞ ተጧጡፏል” ሲልም ገልጿል።
@EyobTikuye @ThiqhEth
"33,764 አቅማቸው ያልደረሱ ሴቶች አርግዘዋል፤ ከእነዚህ ውስጥ 3,368 ተማሪዎች በመሆናቸው ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዋል" - የዝምባብዌ ትምህርት ሚኒስትር
በተለይ በትምህርት ቤት ያለ እድሜ ጋብቻ፣ የልጃገረዶች እርግዝና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የዝምባብዌ ትምህርት ሚኒስትር ድዔታ አንጀሊን ጋታ ገልጸዋል።
በፈረንጆች 2024 ብቻ 33,764 አቅማቸው ያልደረሱ ሴቶች ማርገዛቸውን የተናገሩት ጋታ፣ ከእነዚህ ውስጥ 3,368 ተማሪዎች በመሆናቸው ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዋል ብለዋል።
በተመሳሳይ መልኩ በ2023 ደግሞ 4,000 ተማሪዎች በእርግዝና ምክንያት ከትምህርት ገበታ መገለላቸውን ተናግረዋል።
በመሆኑም ይህን ያለ እድሜ ጋብቻ ችግር ለመቅረፍ የማሰልጠኛ መፅሐፍት መዘጋጀቱንና በድምፅ የታገዘ የግንዛቤ ማስጨበጫ ለመስጠት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ስርጭት መጀመሩን አብራርተዋል።
ዝምባዋብዌ ያለእድሜ ጋብቻን ለመከላከል 40,000 መምህራንን ማሰልጠን መጀመሯም ተገልጿል። #bulawayo24news
@ThiqahEth
ከእርስ በርስ ጦርነት ሸሽተው የተሰደዱ ሱዳናውያን በሊቢያ በረሃ እየሞቱ ነው።
ከቻድ ተነስተው ወደ ሊቢያ ሲጓዙ ከነበሩ 34 ሱዳናውያን ውስጥ ሰባቱ በሊቢያ በረሃ ሙተው መገኘታቸውን የኩፍላ አምቡላንስና ድንገተኛ አደጋ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል።
22 ሰዎችን ከአደጋ ማትረፍ መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አምስቱ ህፃናት ናቸው ተብሏል።
አምስት ስደተኞች እስካሁን ድረስ አልተገኙም ያለው ኩፍላ፣ ካሁን በፊት 260 ሱዳናውያን ህይወት መታደጉን ገልጿል።
787,000 ስደተኞች በሊቢያ እንደሚገኙ አለማቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IMO) መረጃ ያመላክታል።#africannews
@ThiqahEth
"አሜሪካም ፈጣን የታሪፍ መፍትሄን ትፈልጋለች። ማጋነን አይገባም፣ ከአሜሪካ ጋር የጋራ መፍትሔ እንፈልጋለን" - ጀርመን
የጀርመን ምክትል መራሄ መንግስት እና የገንዘብ ሚኒስትር ላርስ ክሊንግቤል አሜሪካ እና አውሮፓ በታሪፍ ተመሳሳይ አቋም እንዳላቸው ተናግረዋል።
"ማጋነን አይገባም፣ ከአሜሪካ ጋር የጋራ መፍትሄ እንፈልጋለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ "አሜሪካም ፈጣን የታሪፍ መፍትሄን ትፈልጋለች" ሲሉ ገልጸዋል።
ጀርመን 183 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ምርቶችን ወደ አሜሪካ በመላክ ከአውሮፓ ተቀዳሚ ሀገር ናት።
የትራምፕ መንግስት በአውሮፓ ምርቶች ላይ 50% ታሪፍ መጣላቸውን አስታውቀዋል። #reuters
@ThiqahEth
5000 ቶን የምትመዝነው የጦር መርከብ በመስጠሟ ሦስት ከፍተኛ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ጉዳዩን "የወንጀል ድርጊት ነው" ሲሉ የሰሜን ኮሪያ ፕሬዝዳንት ጆንግ ኡን ተናግረዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት ቺፍ ሜካኒኩ፣ የግንባታ ወርክ ሾፕ ኃላፊ እና የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ኃላፊ ናቸው።
ሰሜን ኮሪያ የባህር ላይ ጦር መርከብ መስጠሟን ተከትሎ ጥፋተኛ ያለቻቸውን ሦስት ከፍተኛ ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር አውላለች።
የጦር መርከቧ ፕሬዚደንት ኪም ጆንግ ኡን በተገኙበት ስራ ለመጀመር በሂደት ላይ በነበረችበት ወቅት ነው አደጋው የገጠማት ተብሏል።
5000 ቶን የምትመዝነው የጦር መርከብ በገጠማት አደጋ ዙሪያ ምርመራ መጀመሩን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
#dailymirror #thestandard
@ThiqahEth
ተ.መ.ድ በደቡብ ሱዳን የሰላምና ፀጥታ ሁኔታው አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን ገለጸ።
በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ፣ የፖለቲካ ውጥረት ከጀመረበት ከባለፈው የካቲት ጀምሮ የሰብዓዊ እርዳታ መቀነሱን አስታውቀዋል።
በቅርቡ በደቡብ ሱዳን ወታደሮችና በሪክ ማቻር ታማኝ ጦር መካከል ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን የተናገሩት ኮሚሽነሩ፣ ቢያንስ 75 ሰዎች መሞታቸውንና 78 የሚደርሱት መቁሰላቸውን አብራርተዋል።
ባለፉት አራት ወራት በሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ ሱዳናውያን መፈናቀላቸውንም ገልጸዋል።#jursit
@ThiqahEth
#ቪዲዮ፦ ከእስር የተፈቱ የሩሲያ ወታደሮች ባንዲራቸውን በማውለብለብ ታሪክና ባህላቸውን ማክበራቸው ተሰማ።
ከእስር የተፈቱ የሩሲያ ወታደሮች የሩሲያ፣ የሶቪየት ኅብረት እና የሩሲያ ግዛት ባንዲራዎችን በመያዝ በሀገራቸው ታላቅ ታሪክ እንደሚኮሩ አሳይተዋል። #Sputnik
@ThiqahEth
ሩሲያ እና ዩክሬን 1, 000 እስረኞችን ለመልቀቅ ያደረጉት ስምምነት ተጠናቀቀ።
በዛሬው እለት 303 የዩክሬን ወታደሮች ከሩሲያ እስር ቤት ተለቀው ወደ ሀገራቸው ገብተዋል።
ሰሞኑን በመጀመሪያው ዙር 390፣ ትላንት ደግሞ 307 እስረኞችን ተለዋውጠዋል።
በጦርነት ውስጥ የሚገኙት ሩሲያ እና ዩክሬን በቅርቡ በቱርክ ባደረጉት ስብሰባ 1000 እስረኞችን ለመለዋወጥ ተስማምተው ነበር። #kyivpost
ሁለቱ ሀገራት ከሳምንት በፊት አድርገውት የነበረው እስረኞችን የመለዋወጥ ስምምነት፥/channel/thiqahEth/3200
@ThiqahEth
ሩሲያ እና ዩክሬን ለሁለተኛ ጊዜ የእስረኞች ልውውጥ አደረጉ።
ዛሬ ብቻ 307 የሩሲያ ወታደሮች ከዩክሬን ተለቀው ወደ ሀገራቸው ገብተዋል ተብሏል።
ነገር ግን ሩሲያ በዛሬው እለት በዩክሬን ላይ በፈጸመችው ጥቃት 15 ሰዎች መጎዳታቸውን የኪቭ ባለስልጣናት ገልጸዋል። #radiofreeeurope
@ThiqahEth
ሁቲ በእስራኤል አየር መንገድ ላይ በ24 ሰዓት ውስጥ ሦስት ጥቃቶችን ፈጸመ።
ቡድኑ ሀይፐርሶኒክ ሚሳዔልን በመጠቀም የቤንጉሪን አየር መንገድን ኢላማ ማድረጉን አስታውቋል።
የሁቲ ቃል አቀባይ ያህያ ሳሬ፣ "የአየር መንገዱን ሥራ አስተጓጉለናል፤ ግባችንን በሚገባ አሳክተናል" ብሏል።
ስለአየር መንገዱ ጥቃት ከእስራኤል በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም። #anadoluagency
@ThiqahEth
#Ethiopia #FnoteSelam
"የካሶኒና ኦባማ ሹፌሮች፣ በድምሩ 2 ታግተው ተወስደዋል" - የሹፌሮች አንደበት
"በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ዛሬ (15/09/2017 ዓ/ም) ከፍኖተ ሰላም ከተማ በ3 ኪሎ ሜትር እርቀት ከሆዳንሽ ፍኖተ ሰላም መሀል 10 ሰዓት 30 ላይ ካሶኒና ኦባማ ሹፌሮች፣ በድምሩ 2 ታግተው ተወስደዋል።
በሀገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች የአሽከርካሪዎች፣ ረዳቶችና ተሳፋሪዎች እገታ በዝምታ መታየቱ፣ መንግስትም አጋችን ቴክኖሎጅ ተጠቅሞ አሳዶ ለመቅጣት ባለመንቀሳቀሱ፣ አሽከርካሪውም በሙያ አጋሩ የሚደርስን ግፍ አውግዞ መብቱን ለማስከበር ፍትህን ለመጠየቅ ባለመነሳቱ ምክንያት እገታ እንዳይቆም አድማሱን አስፍቶ በየቦታው ብዙዎች እገታን እንደ ክፍት የስራ መስክ ቆጥረው እንዳሻቸው እንዲሆኑ በርን ከፍቷል" ብሏል የሹፌሮችን ውሎ የሚከታተለው የሹፌሮች አንደበት።
@ThiqahEth
"እስካሁን ከ25 ሰዎች በላይ ተገድለዋል" - አቶ አብርሃም አሞሸ
በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ "የጸጥታ አካላት፤ በነዋሪዎች የሚያደርሱት ጥቃት" ትኩረት እንዲሰጠው በተወካዮች ምክር ቤት የዘይሴ ማህበረሰብ ተወካይ አቶ አብርሃም አሞሸ አሳስበዋል።
"ይህንን የልዩ ዞን ጥያቄ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት ዙር ለጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥያቄ አቅርቤያለሁ ይህ አሁን የተጀመረ ሳይሆን ከምርጫ ማግስት ጀምሮ እየተደረገ ያለ ድርጊት ነው" ብለዋል።
ይሁን እንጂ መፍትሄ ባለመገኘቱ፣ "እስካሁን 25 ሰዎች በላይ ተገድለዋል። በየጊዜው ጥያቄዎችን እያነሳን እየተፈጸሙ ያሉ ግድያዎችና ያላግባብ የሚደረጉ እስሮችን ራሳቸው እየፈጸሙ በሕዝቡ ላይና በኢዜማ ፓርቲ እንደተፈጸመ የሚያሳስቡትን ጉዳይ ስናገር ኖሬያለሁ" ነው ያሉት።
"ለሰላም ሚኒስትርም ድረስ ጥያቄ አቅርቤያለሁ፣ አሁንም ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እያቀረብኩ ነው" ብለዋል።
@EyobTikuye @ThiqahEth
"ሁለት ስደተኞች ሙተዋል፤ 186ቱ እስካሁን ድረስ አልተገኙም" - IOM
ዓለማቀፍ ስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ስደተኞችን ጭነው ሲጓዙ የነበሩ 4 ጀልባዎች መገልበጣቸውን አስታውቋል።
ድርጅቱ ስደተኞቹ 57 ሴቶችን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ገልጿል።
IOM ባለፈው የፈረንጆች አመት 2024 ውስጥ 558 ስደተኞች ከምስራቅ አፍሪካ ተነስተው ጅቡቲና የመንን ለማቋረጥ ሲሞክሩ ህይወታቸው ማለፉን አመላክቷል።
#thedailytribunenewsofbahrain #vaticannews
ThiqahEth
#Ethiopia #Gambella
ስድስት ሰዎች በሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች መገደላቸው ጋምቤላ ክልል ገለጸ።
የደቡብ ሱዳን መርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ድንበር ጥሰው በመግባት ባደረሱት ጥቃት ንጹሐን መገደላቸውን የጋምቤላ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ነግሮናል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ኦጁሉ ጊሎ፣ ከትላንት ወዲያ ጠዋት ታጣቂዎቹ በከፈቱት ተኩስ 4 ወንዶችና ሁለት ሴቶች መገደላቸውን ገልጸዋል።
ኃላፊው፣ “ታጣቂዎቹ ከብት መዝረፍ፣ ህፃናት መውሰድ የለመደባቸው ትሬንድ ነው። ትላንት ባሱ የተመታበት ቦታ ብዙ ጊዜ የወረዳው ከፍተኛ አካላት ትኩረት የሚያደርበት ነው። ግን የትላንቱ ክስተት በአጋጣሚ ከባድ ነበር” ብለዋል።
ቢሮው ከወር በፊት በሰጠን ቃል፣ “ በተለይ በዚህ ወርና እስከ ሚያዚያ መጨረሻ ድረስ ታጣቂዎቹ የሚፈታተኑንበት ወቅት ነው። ኩሬዎች ስለሚደርቁ ለእነርሱ መምጣት አመቺ ይሆናል። አሁን ትንሽ፣ ትንሽ ምልክቶችን እያየን ነው። እየመጡ ነው" ብሎ ነበር።
የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ከደቡብ ሱዳን ተነስተው የጋምቤላ ክልልን ድንበር ጥሰው በመግባት ልጆችን፣ ከብቶችን ሰርቀው በመውሰድ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጽሙ ይታወቃል። Read More፡ /channel/tikvahethiopia/97152
@ThiqahEth @TikvahEthiopia
"የህልውና ጉዳይ ስለሆነ እስራኤል አማራጭ የላትም ጦርነቱን ትቀጥላለች" - አምባሳደር አብረሃም ንጉሴ
በኢትዮጵያ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የእስራኤልን 58ኛ አመት የነፃነት ቀን ዛሬ አክብሯል።
ይህም "የእየሩሳሌም ቀን" ተብሎ ይጠራል። የእየሩሳሌም ቀን ማለት፣ እስራዔላዊያን በአረብ፣ እንግሊዝ፣ ኦቶማን ቱርክ አስተዳደር ስር ከቆየ ከ2000 ዓመታት በኋላ የኢየሩሳሌም ቅዱስ ስፍራን ተረክበው ማስተዳደር የጀመሩበት ቀን ነው።
በመርሀ ግብሩ የተገኙት በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብረሃም ንጉሴ፣ ከቲቃህ ኢትዮጵያ ጋር ባደረጉት በቆይታ ምን አሉ?
"እስራኤል ከአንድ አመት ተኩል በላይ በጦርነት ነው ያለችው። ይሄን ጦርነት ፈልጋው አይደለም የገባችው፣ ተደፍራ፣ ዜጓቿ ታርደው ነው።
በአሸባሪው ሀማስ ጥቃት ደርሶባት፣ የታፈኑ ዜጎቿን ለማስመለስ ነው። በእስራኤል ላይ በሰባት አቅጣጫ ነው ጦርነት የተከፈተው።
እነዚህ ሁሉ በኢራን አስተባባሪነት ነው የተከፈቱት። ስለዚህ እስራኤል የህልውና ጉዳይ ስለሆነ አማራጭ የላትም መከላከል አለባት" ብለዋል።
(ተጨማሪ አለን)
@EyobTikuye @ThiqahEth
"ዩክሬን የሩሲያን ሲቪልና ማኀበራዊ መሰረተ ልማቶች ኢላማ አድርጋለች፤ በዩክሬን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች አጸፋዊ እርምጃዎች ናቸው" - ዲሚትሪ ፔስኮቭ
የሩሲያና ዩክሬን ንግግርን ለማስቀጠል አሁንም መግባባት ላይ እንዳልተደረሰ፣ ለቀጣዩ ዙር መዘጋጀት እንደሚገባ ክሬምሊን ገለጸ።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ምን አሉ?
"ዩክሬን የሩሲያን ሲቪልና ማኀበራዊ መሰረተ ልማቶች ኢላማ አድርጋለች፤ በዩክሬን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች አጸፋዊ እርምጃዎች ናቸው።
የዩክሬን የድርድር ሂደት መጀመሩ ስኬት ነው፤ ሩሲያ ሂደቱን ስላመቻቹ ለትራምፕ እና ለዩናይትድ ስቴትስ ምስጋና ታቀርባለች፡፡
በአሜሪካ እና በሩሲያ መካከል ውጤታማ የሁለትዮሽ ግንኙነትን እንደገና የመገንባት ሂደት እየተጀመረ ነው።
የንግድ ተወካዮች በዛሬው እለት ከፑቲን ጋር በሚያደርጉት ስብሰባ ስለ ሥራቸው እና የልማት እቅዶች ይወያያሉ።
ፑቲን ከቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊዳን ጋር ዛሬ ይገናኛሉ። የፊዳን ጉብኝት በሩሲያ እና ቱርክ የሁለትዮሽ ግንኙነት ትኩረቱን ያደርጋል" ማለታቸውን #ስፑትኒክ ዘግቧል።
@ThiqahEth
"ቀጥተኛ ድርድር አድርገናል። አጥጋቢ ስምምነት ላይ ለመድረስ ጊዜ ያስፈልጋል" - ትራምፕ
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በአውሮፓ ላይ የጣሉትን የ50% ታሪፍ ለወር አራዘሙ።
ከአውሮፓ ህብረት ፕሬዝዳንት ኦርሱላ ቮንደርሊን ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ ሰኔ ላይ ይተገበራል ያሉት ውሳኔ ወደ ሐምሌ እንዲዛወር መወሰናቸውን ገልጸዋል።
"ቀጥተኛ ድርድር አድርገናል" ያሉት ትራምፕ "አጥጋቢ ስምምነት ላይ ለመድረስ ጊዜ ያስፈልጋል" ሲሉ የተራዘመበትን ምክንያት አብራርተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ከአውሮፓ በሚገቡ ምሬቶች ላይ የጣሉት ቀረጥ ባለፈው ሳምንት ከ30% ወደ 50% ከፍ ማድረጋቸው ይታወቃል።#irishexaminer
@ThiqahEth
#Ethiopia
“ፓሊሲዎቹ ድሃን ከድህነት ማውጣት አልቻሉም፤ ድህነትን ለመቀነስ ያመጡት ውጤትም ከዜሮ ያንሳል”- የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክ አሶሴሽን
የኢትዮጵያ መንግስት ለ22 ዓመታት ድህነትን ለመቀነስ ያወጣቸው ፓሊሲዎች ውጤት ከዜሮ እንደሚያንስ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክ አሶሴሽን ጥናት አመለከተ።
አሶሴሽኑ እ.ኤ.አ ከ2001 እስከ 2023 ያለውን የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አፈጻጸምን የተመለከተ ጥናት ሰሞኑን ይፋ ማድረጉን ሪፓርተር አስነብቧል።
ኢትዮጵያ እያደጉ ካሉ አገሮች አንዷ የነበረች ቢሆንም፣ ከ2011 ዓ/ም ጀምሮ የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ ማሽቆልቆሉን ጥናቱ መለየቱን ተገልጿል።
ግጭቶች፦
₀የ10 አመታት የልማት እቅድ በአግባቡ እንዳይተገበር፣
₀ኢኮሚኖሚ እንዳይረጋጋ፣
₀ድህነት እንዲጨምር፣
₀ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲቀንስ፣
₀ሥራ አጥነት እንዲጨምር ማድረጋቸው በጥናቱ ተለይቷል።
ግብርና ለሀገራዊ ጠቅላላ ምርት ያለው አስተዋጽኦ በተለይ እ.ኤ.አ በ2024 እና 2025 አንድ ሦስተኛ ድርሻ እንዳለው፣ ይሁን እንጂ የመቀነስ ምጣኔ አሁንም እንደሚቀረው ዘገባው ጠቅሷል።
"ሆኖም የሀገሪቱ 32.4 በመቶ ኢኮኖሚ ለሚያስገኘው የግብርና ዘርፍ የብድር መጠን አነስተኛ በመሆኑ በተለይ እ.ኤ.አ ከ2012 ጀምሮ መጠኑ እየቀነሰ ከ3 በመቶ ማነሱ ተጠቅሷል" ተብሏል። #Reporter
@ThiqahEth
#Amhara #Gojam
"ስምንት ሹፌርና ረዳቶች ታግተዋል" - የሹፌሮች አንደበት
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም በ17/09/2017 ዓ/ም ከ ዱርቤቴ ወተት አባይ (ቢኮሎ አባይ) መካከል ድብካን ጊዮርጊስ የሚባል ልዩ ቦታ ከቀኑ 8 ሰዓት 30 ገደማ 3 ኦባማ 1 ካሦኒ ሾፌርና ረዳት/በድምሩ 8 ረዳትና ሹፌር ታግተው መወሰዳቸውን የሹፌሮች አንደበት ገልጿል።
በምዕራብ ጎጃም ከ3 ቀና በፊት፣ ፍኖተ ሰላም አካባቢ ከ5 ቀን በፊት ከእንጅባራ ቻግኒ መንገድ እገታ መፈጸሙን አስታውሶ፣ "አሽከርካሪዎች ጥንቃቄን አድርጉ" ሲል አሳስቧል።
@ThiqahEth
ትራምፕ 60 ቢሊዮን ዶላር በማገዳቸው ከ150 ሺሕ በላይ የሄይቲ ዜጎች በኤችአይቪ ተጠቂ መሆናቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት (USAID) በጀት መቋረጥን ተከትሎ በሄይቲ የኤችአይቪ መድኃኒት እጥረት አጋጥሟታል።
ትራምፕ አሜሪካ ለውጭ እርዳታ ከምትመድበው በጀት 90% የሚሆነውን የዩኤስኤይድ ድጎማ በማቋረጣቸው ለአለማቀፍ እርዳታ ሊለቀቅ የነበረ 60 ቢሊዮን ዶላር አግደዋል።
ይህን ተከትሎ የእረዳታው መቋረጥ ጫና ከፈጠረባቸው ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ሄይቲ በአሁኑ ወቅት ከ150,000 በላይ የሚሆኑት ዜጎቿ የበሽታው ተጠቂ መሆናቸው ተገልጿል።
ካረቢያኗ ሄይቲ ከ2023 ወዲህ "በወሮበላ" ቡድኖች እየታመሰች ትገኛለች። #africannews
@ThiqahEth
እስራኤል በዛሬው ዕለት በፈጸመችው ጥቃት 23 ሰዎች ተገደሉ።
ከሟቾቹ ውስጥ ጋዜጠኞችና የእርዳታ ጊዜ ሰራተኞች እንደሚገኙበት ተገልጿል።
ጥቃቱ በካሃን የኑስ፣ በጃባሊያ እና ኑስራት ከተሞች ነው የተፈጸመው። #theindependent
@ThiqahEth
#Ethiopia #የዝንጀሮፈንጣጣ
“የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በሕመማሙ መያዛቸው ከተጠረጠሩ ታማሚዎች በወሰደው ናሙና በMpox ቫይረስ የተያዘ ሰው ማግኘቱን አረጋግጧል” - ኢንስቲትዩቱና ሚኒስቴሩ
በኢትዮጵያ የዝንጀሮ ፈንጣጣ/Mpox የተያዘ ሰው መገኘቱን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትና ጤና ሚኒስቴር የጋራ መግለጫቸው ዛሬ አስታውቀዋል።
በቫይረሱ የተጠቃው የ21 ቀን እድሜ ህፃን ሲሆን እናቱም ለቫይረሱ መጋለጣቸው በምርመራ መረጋገጡ ተነግሯል።
(የጋራ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@ThiqahEth
"ከአሜሪካ ሁሉን አቀፍ የንግድ ጦርነት ተከፍቶብናል" - የአውሮፓ ህብረት ንግድ ኮሚሽን
የአውሮፓ ህብረት የንግድ ኮሚሽን"አውሮፓን ለማዳን አራት ሳምንታት አሉን" ሲል ገለጸ።
የህብረቱ የንግድ ኮሚሽነር ማሮስ ሰቭኮቪች "ከአሜሪካ ሁሉን አቀፍ የንግድ ጦርነት ተከፍቶብናል" ሲሉ ተናግረዋል።
አሜሪካ በአውሮፓ ገበያ ላይ 50% ቀረጥ መጨመሯን ያስታወቁት ሰቭኮቪች "አውሮፓን የምናድንበት ወሳኝ ጊዜ ላይ እንገናኛለን"ብለዋል።
የትራምፕ አስተዳደር የጣለው ታሪፍ "ምክንያታዊ እና ግልጽነት የጎደለው ነው" ሲሉ ተችተዋል። #independent
@ThiqahEth
"በዓለም አቀፍ ደረጃ 500,000 ሰዎች የፊስቱላ ተጠቂ ናቸው" - ተመድ
በተመድ የስነተዋልዶ ጤና ዳይሬክተር ሲማ ባሁስ፣ "ዝምተኛ ገዳይ" ሲሉ የጠሩት የፊስቱላ በሽታ በአሁኑ ወቅት ትልቅ የጤና ስጋት ሆኗል ብለዋል።
"በዓለም አቀፍ ደረጃ 500,000 ሰዎች የፊስቱላ ተጠቂ ናቸው" ነው ያሉት።
ባሁስ ከ2003 እስከ 2024 ባሉት 21 አመታት 150,000 ለሚሆኑ ሴቶች የፊስቱላ ህክምና መደረጉን ተናግረዋል። #peoplesgazette
@ThiqahEth
ትራምፕ በአውሮፓ ገበያ ላይ የ50% ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ።
ካሁን በፊት ጥለውት ከነበረው 30% ወደ 50% ከፍ ለማድረግ መወሰናቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የታሪፍ ውሳኔ ከመጪው ሰኔ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።#kyivpost
@ThiqahEth
#EthiopianHealthProfessionals
"ሁሉም የጤና ተቋማት ላይ ሙሉ አገልግሎት እየተሰጠ ነው" - ጤና ሚኒስቴር
"በተለያዩ ክልሎች በተለይ በትግራይ ክልል በሁሉም ጤና ተቋማት በሚባል ደረጃ ሥራ ቆሟል" - ጤና ባለሙያዎች
ብሔራዊ ቴሌቪዥን በዘገባው ምን አለ?
"ባለፉት ቀናት አልፎ፣ አልፎ በአንዳንድ የሥራ ክፍሎች የነበሩ የሥራ መስተጓጎሎች አሁን በመላ ሀገሪቱ በሙሉ ወደ ሥራ መገባቱን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
ከሰሞኑ የተፈጠረውን ክስተት መነሻ በማድረግ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው የሚኖሩ ችግሮችን ለመፍታት ሰፊ ውይይቶች እየተደረጉ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ተናግረዋል።
የህክምና ባልሞያዎች ያሏቸውን ጥያቄዎች ሁሉ ሥራቸውን በአግባቡ እያከናወኑ መጠየቅ እንዲችሉ ማድረግ ሊለመድ የሚገባ ነው ያሉት ዴዔታው መንግስትም ጥያቄዎችን ለመመለስ እየሰራ መሆኑ ተናግረዋል።
በሥራ ያሉትን ባለሞያዎች አመስግነናል ህብረተሰቡም በብዛት ወደ ህክምና ተቋማት መሄዱን ተመልክተናል። እንዲህ አይነት ክስተቶች በሴክተራችን በድጋሜ እንዳይመጣ በቀጣይነት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል" ብሏል።
የጤና ባለሙያዎች ደግሞ፣ "በተለያዩ ክልሎች በተለይ በትግራይ ክልል በሁሉም ጤና ተቋማት በሚባል ደረጃ ሥራ ቆሟል" ብለውናል።
@ThiqahEth
#DebubEthiopia #GamoZone
“በዘይሴ ብሔረሰብ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ በደሎች እጅግ በጣም ሰፊ ናቸው። አንዱ ህዝቡን አሳዶ በጦር መሳሪያ መግደል ነው” - የፓርላማ አባል
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዘይሴ ማህበረሰብ ተወካይ አቶ አብርሃም አሞሸ፣ "በዘይሴ ብሔረሰብ ላይ እየተፈጸሙ ያሉ በደሎች እጅግ በጣም ሰፊ ናቸው። አንዱ ህዝቡን አሳዶ በጦር መሳሪያ መግደል ነው" አሉ።
"ከዛ ባለፈ አሁን የነዋሪዎቹን ቤቶቻቸውን እያቃጠሉባቸው ነው" ያሉት የምክር ቤት አባሉ፣ "በተለይ ከግንቦት 3/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስካሁን ህዝቡ መፈናቀል ላይ ነው" ብለዋል።
"የጋሞ ዞን መደበኛ ፓሊስ፣ በኢመደበኛ አደረጃጀት በጋሞ በተደራጁ በቀድሞ የጦር ተመላሽ አባላት፣ በሚሊሻዎች በአጠቃላይ የዘይሴን ህዝብ ከገዛ ከዘይሴ ምድር ላይ አጥፍቶ ምድሩን የመውረስ ነው ስትራቴጂ ቀይሰው እየሰሩ ያሉት” ነው ያሉት።
ችግሩ ከምርጫ ጀምሮ በየወቅቱ እየተከሰተ የቆዬና ያለ እንደሆነ፣ ከዚህ ቀደም በፓርላማ ተገኝተው ደጋግመው ትኩረት እንዲሰጥ ለጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጭምር ቢያሳስቡም መፍትሄ እንዳልተሰጠ ተወካዩ ገልጸዋል።
መፍትሄውን በተመለከተም፣ ጥቃት እየተፈጸመበት ባለው ቦታ ገለልተኛ የሆኑት ፌደራል ፓሊስና መከላከያ ሠራዊት በአስቸኳይ እንዲመደቡ አሳስበዋል።
@EyobTikuye @ThiqahEth
ሶሪያ!
በሶሪያ የሟቾች ቁጥር 600 ደረሰ።
በሶሪያ የሽግግር መንግስት እና በአሳድ ታማኝ ኃይሎች መካከል የሚደረገው ጦርነት ዛሬም ቀጥሏል።
ሁሉም ሟቾች የቀድሞው ፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ የዘር ሀረግ የሚመዘዝበት የአልዋይቲ አናሳ ማህበረሰብ አባል መሆናቸው ተገልጿል።
በጦርነቱ ከፍተኛ የቤትና ንብረት ዘረፋ እየተፈጸመ ነው ተብሏል። #burnabynow
@ThiqahEth